×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
አዋጅ ቁጥር 233/93 የፌዴራል የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ማቋቋሚያ አዋጅ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን መርምሮ ውሳኔ የሚሰመ ዓንደገና የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሰባተኛ ዓመት ቁጥር ፲፰ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አዲስ አበባ - የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፫ / ፲፱፻፶፫ ዓም • የፌዴራል የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ማቋቋሚያ ገጽ ፩ሺ፪፻፳፯ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፫ ፲፱፻፫ ዓም የፌዴራል የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ በሕግ ተለይተው በፌዴራሉ መንግሥት እንዲሰበሰቡ በተመደቡ የግብር ውሳኔዎች ላይ በግብር ከፋዮች በይግባኝ ማቋቋም በማስፈለጉ ፤ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፵፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ክፍል አንድ አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የፌዴራል የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፫ / ፲፱፻ቹ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ . ትርጓሜ በዚህ አዋጅ ውስጥ ፤ ፩ . “ ግብር ” ማለት ከቴምብር ቀረጥ በገቢና ወጪ | 2. Definitions ዕቃዎች ላይ ከሚጣሉ ቀረጦችና ታክሶች በስተቀር በፌዴራል መንግሥት እንዲሰበሰብ የተመደበ ማንኛ ቸውም ግብር ወይም ታክስ ነው ፣ ፪ . “ ባለሥልጣን ” ማለት የፌዴራል መንግሥት የአገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን ነው ፣ ፫ . “ ጉባዔ ” ማለት የፌዴራል የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ፬ . “ ሰው ” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖ.ሣ.ቁ : ፰ሺ፩ ገጽ ፭ሺ፬፻፷፰ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፰ የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻ ዓም ክፍል ሁለት ስለ ግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ፫ . ስለመቋቋም ፩ . የፌዴራል ግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ / ከዚህ በኋላ “ ጉባዔው ” በመባል የሚጠራ ራሱን የቻለ የሕግ ሰውነት ያለው የፌዴራል መንግሥት አካል ሆኖ ተቋቁሟል ። ፪ • የጉባዔው ተጠሪነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሆናል ። ዋና መሥሪያ ቤት የጉባዔው ዋና መሥሪያ ቤት አዲስ አበባ ሆኖ ጉባዔው በሚወስነው በአገሪቱ በማናቸውም ሥፍራ ቅርንጫፍ ጽ / ቤቶች ሊኖሩት ይችላል ። ፪ • ጉባዔው ባልተቋቋመበት ክልል የሚገኘው የክልል መስተዳድር የግብር ይግባኝ ሰሚ አካል ጉባዔው በሚሰጠው ውክልና መሠረት በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፮ የተደነገገው ተጨማሪ ሥልጣን ይኖረዋል ። ፭ ዓላማ የጉባዔው ዓላማ ባለሥልጣኑ በሚወስነው ግብር ላይ በግብር ከፋዮች በይግባኝ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን መርምሮ መወሰን ይሆናል ። ፮ • የጉባዔው ሥልጣንና ተግባር ማንኛውም በዚህ አዋጅ መሠረት የተቋቋመ ጉባዔ የሚከ ተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል ፤ ፩ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፪ / ሀ / መሠረት የሚመሩለትን የይግባኝ ጉዳዮች መርምሮ ይወስናል ፣ ፪ የቀረበለትን ጉዳይ ለመወሰን አግባብነት ያለውን ማንኛውም መዝገብ ወይም ሰነድ እንዲቀርብለት፡ ማንኛውም ሰው ቀርቦ የሚጠየቀውን ማንኛውንም አስፈላጊ መረጃ እንዲሰጥ ያዛል ፣ ባለሥልጣኑ አስተላልፎት የነበረውን የግብር ውሳኔ ለማጽደቅ ፣ ለመቀነስ ፣ ለመጨመር ወይም ለመሠረዝ ይችላል ። እንደዚሁም ለጉዳዩ ፍጻሜ ተገቢ ሆኖ ያገኘውን ትዕዛዝ ይሰጣል ፣ ሆኖም ጉባዔው ውሳኔውን ሊሰጥ የቻለበትን ምክንያት በውሳኔው ማስፈር ይኖር ፬ ጉባዔውየሰጠውን ውሣኔ ግልባጭ ለተከራካሪ ወገኖች እንዲደርስ ያደርጋል ። ፯ : የጉባዔው የውሳኔ አሰጣጥ ሥርዓት ፩ . ከጉባዔው አባላት ሦስቱ ሲገኙ ምልዓተ ጉባዔ ይሆናል ። ጉባዔው በቀረቡለት የይግባኝ ጉዳዮች ላይ በድምጽ ብልጫ ውሳኔይሰጣል ። ድምጽእኩል በእኩል የተከፈለ እንደሆነ ሰብሳቢው ወሳኝ ድምጽ ይኖረዋል ። ፫ በሃሳብ የተለየ የጉባዔው አባል የሀሳብ ልዩነቱን በውሳኔው ያሰፍራል ። ፰ : የጉባዔው አቋም ፩ የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔው ፤ ሀ ) ፕሬዚዳንት ፣ ለ ) የጉባዔ አባላት ፣ ሐ ጽሕፈት እና አስፈላጊ የሆኑ ሠራተኞች ፣ ይኖሩታል ። ፪ • የጉባዔው ፕሬዚዳንት በመንግሥት ይሾማል ። ፱ • የጉባዔው ፕሬዚዳንት ሥልጣንና ተግባር የጉባዔው ፕሬዚዳንት የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል ፤ ፪ የጉባዔው ፕሬዚዳንት በመንግሥት ይሾማል ። ገጽ ፭ሺ፬፻፷፬ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፰ የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፰ ዓም • የጉባዔው ሰብሳቢ ሆኖ ይሠራል ፣ ፪ ለየጉባዔዎቹ ሰብሳቢ ይሰይማል ፤ አባላትን ይደለድላል ፣ ፫ በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ መሠረት የጽ / ቤቱን ሠራተኞች ይቀጥራል ፣ ያስተዳድራል ፣ ፬ የጉባዔውን ዓመታዊ በጀትና የሥራ ፕሮግራም አዘጋጅቶ ያቀርባል ፣ ለጉባዔው በተፈቀደው በጀትና የሥራ ፕሮግራም መሠረት ገንዘብ ወጪ ያደርጋል ፣ ፮ ከሌሎች ወገኖች ጋር በሚደረጉ ግንኙነቶች ሁሉ ጉባዔውን ይወክላል ፣ ፯ . ለጉባዔው አባላት የሚከፈለውን አበል ያስወስናል ፣ ለጽ / ቤቱ ሥራ ቅልጥፍና በሚያስፈልግ መጠን ሥልጣንና ተግባሩን በከፊል ለጽ / ቤቱ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በውክልና ይሰጣል ፣ ስለ ጉባዔው የሥራ እንቅስቃሴ በየዓመቱ መጨረሻ ወይም አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ያቀርባል ። ስለጉባዔው አባላት ፩ . እያንዳንዱ ጉባዔ አምስት አባላት የሚኖሩት ሲሆን ፤ ከአባላቱ መካከል አንድ ሰብሳቢና እርሱ በማይኖርበት ጊዜ ተክቶ የሚሠራ ምክትል ሰብሳቢ ይኖረዋል ፣ ጉባዔው ከንግዱ ኅብረተሰብ የሚወከሉ አባላት የሚኖሩት ሲሆን ፣ የተወካይ አባላቱ ቁጥርና የሚወከ ሉበት ሥርዓት በመመሪያ ይወሰናል ፣ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ሌሎች አባላት በጉባዔው ፕሬዚዳንት አቅራቢነት በመንግሥት ይሾማሉ ፤ የጉባዔው አባላት የአገልግሎት ዘመን አራት ዓመት ይሆናል ። ሆኖም ማንኛውም የጉባዔ አባል ለተጨማሪ አንድ የአገልግሎት ዘመን ሊመረጥ ወይም ሊሾም ይችላል ። ፲፩ . የጉባዔው ሰብሳቢ ሥልጣንና ተግባር የጉባዔው ሰብሳቢ ፤ የይግባኝ ክርክር በሚሰማበት ወቅት በሰብሳቢነት | 11. Powers and Duties of the Chaimman of the the Tribunal . ይመራል ፣ ሥነ ሥርዓት መጠበቁን ይቆጣጠራል ፣ በቃለ ጉባዔ የሚያዙ ወይም በውሳኔ ውስጥየሚመዘገቡ የቃል ወይም የጽሑፉ ክርክሮች ሁሉ በሚገባ መያዛቸ ውንና መዘጋጀታቸውን ያረጋግጣል ። ፲፪ : ስለ ጉባዔው ጽሕፈት ቤት የጽሕፈት ቤቱ ተጠሪነት ለፕሬዚዳንቱ ይሆናል ። ጽሕፈት ቤቱ ፤ ሀ ) ባለሥልጣኑ ያስተላለፋቸውን የግብር ውሳኔዎች በመቃወም በሚቀርቡ ይግባኞች በዚህ ሕግ ይግባኝ ስለማቅረብ የተመለከቱት ሁኔታዎች ተሟልተው መቅረባቸውን በማረጋገጥ ይቀበላል ፣ ለ ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፪ ( ሀ ) የተቀበላቸውን ይግባኞች በሰባት የሥራ ቀናት ውስጥ ለጉባዔው ይመራል ፣ ሐ ) የጉባዔውን ውሳኔዎችና ሰነዶች ይጠብቃል ፣ ለጉባዔው አስፈላጊውን አስተዳደራዊ ድጋፍ ይሰጣል ፣ መ ) ከጉባዔው ፕሬዚዳንት የሚመሩለትን ሌሎች ተግባሮች ያከናውናል ። ፲፫ በጀት ጉባዔው በፌዴራሉ መንግሥት በሚመደብለት በጀት ይተዳ ፲፬ • የሂሣብ መዛግብት ጉባኤው የተሟሉና ትክክለኛ የሆኑ የሂሣብ መዛግብት ይይዛል ። የጉባዔው ሂሣብ በዋናው ኦዲተር ወይም እርሱ በሚወ 1 2 ) The account of the tribunal shall be audited annually by ክለው ኦዲተር በየዓመቱ ይመረመራል ። ክፍል ሦስት ስለ ይግባኝ ፲፭ ይግባኝ ለማቅረብ መሟላት ስላለባቸው ሁኔታዎች ባለሥልጣኑ ያስተላለፈውን የግብር ውሳኔ በመቃወም የሚቀርብ የይግባኝ ማመልከቻ በጽሑፍ ሆኖ ቢያንስ በሦስት ቅጂዎች መቅረብ ይኖርበታል ። ፪ ግብር ከፋዮች ይግባኝ ለማቅረቢያ በአንቀጽ ፲፮ የተወ ሰነው ጊዜ ኲማለፉ በፊት ለሚቀርበውይግባኝመክፈቻ ከዚህ በታች የተመለከተውን ገንዘብ ባለሥልጣኑ ዘንድ ማስያዝ አለባቸው ፤ ሀ ) በባለሥልጣኑ ከተወሰነው ግብር ሂሣብ ላይ ፪፭ ፐርሰንት ( ሰባ አምስት በመቶ ) ወይም ለ ) በይግባኝ ባዩ ላይ ባለፈው የግብር ዘመን የመጨ ረሻው ግብር ታስቦ ከተወሰነው ልክ ላይ ፻፭ ፐርሰንት ( ሰባ አምስት በመቶ ) ፣ በመያዣነት የሚከፈለው ገንዘብ ከዚህ በላይ በተጠቀሰው ሁኔታ ሲታሰብ ዝቅተኛ የሆነው በቂ ነው ። ሐ ) የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) ( ለ ) ድንጋጌ ቢኖርም ፣ በመያዣ የሚከፈለው ገንዘብ ፣ ግብር ከፋዩ ባስታወቀው ግብር የሚከፈልበት ገቢ ላይ ሊከፈል ከሚገባው በማናቸውም ምክንያት ማነስ የለበትም ። መ ) ግብር ከፋዩ ግብር እንዲከፍል የተጠየቀው ለመ ጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ለመያዣ የሚከፈለው ገንዘብ ቢያንስ ቢያንስ ባስታወቀው ገቢው ላይ ሊከፈል የሚገባውን ግብር ወይም የገቢውን ማስታወቂያ አላቀረበ እንደሆነ እንዲከፍል ከተ ጠየቀው ግማሹን ( H ፐርሰንት ) ለባለሥልጣኑ መክፈል አለበት ። ሠ ) ከዚህ በላይ የተመለከቱት ድንጋጌዎች ቢኖሩም በሽያጭና ኤክሳይዝ ታክስ አዋጅቁጥር፳፰ ፳፭ ( እንደተሻሻለው ) መሠረት ተወስኖ በተጠየቀው ታክስ ላይ ለሚቀርበው ይግባኝ ለባለሥልጣኑ የሚከፈለው የመያዣ ገንዘብ ከተወሰነው ታክስ ከፃ ፐርሰንት ( ሀምሣ በመቶ ) ማነስ የለበትም ። ፲፮ • ይግባኝ የማቅረቢያ ጊዜ ፩ ይግባኝማቅረብ የሚቻለው የግብሩ ውሳኔ ማስታወቂያ ለግብር ከፋዩ ከተሰጠበት ቀን አንስቶ በሰላሣ ቀን ውስጥ ነው ። ፪ ግብር ከፋዩ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) በተመለ ከተው ጊዜ ውስጥይግባኙን ካላቀረበ ወይምከዚህ በላይ በአንቀጽ ፲፭ የተመለከተውን ማስያዣ ሳያሲዝ ወይም ሳይከፍል የቀረ እንደሆነ በባለሥልጣኑ የተወሰነው ግብር ትክክለኛና የመጨረሻ ሆኖ ወዲያውኑ ተፈጻሚ ይሆናል ። ፲፯ ስጉባዔው በሚሰጥ ውሳኔ ላይ ይግባኝ ስለማቅረብ ባለሥልጣኑ ወይም ግብርከፋዩ ጉባዔውየሰጠው ውሳኔ ሕግ ነክ በሆነ ጉዳይ ላይ በመሳሳቱ ቅር የተሰኘእንደሆነ ጉባዔው ውሳኔ ከሰጠበት ቀን አንስቶ በሰላሳ ቀናት ውስጥ ይግባኙን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍ / ቤት ማቅረብ ይኖርበታል ። ፪ . በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) መሠረት ይግባኙ የቀረበለት ፍርድ ቤት በሕግ ረገድ የተነሣውን ክርክር በመመርመር የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ካገኘው የተሳሳተውን የሕግ ጉዳይ አቃንቶ ውሳኔውን ለሁለቱ ወገኖች በማሳወቅ ለጉባዔው ይመልሰዋል ። ገጽ ፭ሺ፬፻፷፩ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፰ የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፫ ዓ.ም. Federal Negarit Gazeta ፍርድ ቤቱ በማናቸውም ሁኔታ የግብር ትመናውን አስመልክቶ ውሳኔ መስጠት አይችልም ። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ ላይ የሚቀርብ ይግባኝ ፍ / ቤቱ በይግባኝ በተመለከተው ጉዳይ ላይ ብቻ የተወሰነ ይሆናል ። ፲፰ : ስለ ውሳኔ አፈጻጸም ፩ በጉባዔው በተሰጠ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ ይግባኝ የጉባ ዔውን ውሳኔ አፈጸጸም አያግደውም ። ፪ • የግብሩ ግምት በመጨረሻው የፍርድ ቤት ውሳኔ መሠረት የተሻሻለ ወይም የተለወጠ እንደሆነ ፣ ሀ ) ከሚገባው በላይ ተከፍሎ እንደሆነ በተጨማሪ የተከፈለው ለግብር ከፋዩ ወዲያውኑ ይመለሳል ፣ ለ ) ግብር ከፋዩ መክፈል ከሚገባው በታች ግብር ከፍሎ እንደሆነ ተጨማሪውን ገንዘብ ወዲያውኑ ይከፍላል ። ክፍል አራት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ፲፱ • የመተባበር ግዴታ ማንኛውም ሰው ይህን አዋጅ በማስፈጸም ረገድ ከግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ጋር የመተባበር ግዴታ አለበት ። ፳ የመሸጋገሪያ ድንጋጌ ፩ . ይህ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በባለሥልጣኑ በተወሰነ ግብር መነሻ በግብር ይግባኝ ጉባዔ በመታየት ላይ ያሉ ጉዳዮች በዚህ አዋጅ መሠረት በተቋቋመው ጉባኤ ይታያሉ ። ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች በዚህ አዋጅ መሠረት በተቋቋመው ጉባዔ እንደተሰጡ ውሳኔዎች ይቆጠራሉ ። ፳፩ : ተፈጻሚነት የሌላቸው ሕጎች ፩ ከማናቸውም ገቢ ግብር ስለማስከፈል የወጣው አዋጅ ቁጥር ፩፻፷፫ / ( እንደተሻሻለው ) ከአንቀጽ ፴፱ እስከ አንቀጽ ፰፩ ( ጨምሮ ) ያሉት ድንጋጌዎች ፣ እና ፪ : ይህን አዋጅየሚቃረኑማናቸውም ሕጎች ወይምደንቦች በዚህ አዋጅ ውስጥ የተሸፈኑ ጉዳዮችን በተመለከተ ተፈጻሚነት አይኖራቸውም ። ፳፪ አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከየካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓም ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ የካቲት ፳፱ ቀን ፲፱፻ ዓም ዶ / ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?