×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጄንሲ ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ.. ገጽ ፫ሺ፪፻፲፯

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እስራ ሦስተኛ ዓመት ቁጥር ፭ አዲስ አበባ - ህዳር ፲፭ ቀን ፲፱የህ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ የኢንፎርሜሽን ደኅንነት ኤጄንሲ ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ .. ገጽ ፫ሺ፪፻፮ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፩፻፴ / ፲፱፻፳፱ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲን ለማቋቋም የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የሚኒስትሮች የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር ፬፻፸፩ / ፲፱፻፵፰ አንቀጽ ፭ መሠረት ይህን ደንብ አውጥቷል ፡፡ ፩ . አጭር ርዕስ ይህ ደንብ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ | Republic of Ethiopia Proclamation No. 47 1/2006 . ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፩፻፬ / ፲፱፻ህ " ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ፡፡ ፪ . ትርጓሜ በዚህ ደንብ ውስጥ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም ካላሰጠው በስተቀር ፤ ፩ . " ቁልፍ ተቋም " ማለት ለኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አደጋ የተጋለጠና በሚፈጠረው አደጋም በሀገሪቱ ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ ጥቅሞች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያመጣ የሚችል ተቋም ነው ፧ ፪ . " የኮምፒውተር ደህንነት " ማለት የኮምፒውቲንግ ፕላትፎርም ደህንነት ለማረጋገጥ ከኮምፒውተር አጠቃቀም ጋር የተያያዙ ስጋቶችን መቆጣጠር ያንዱ ዋጋ ፖ.ሣ.ቁ. ፰ሺ፩ ገጽ ፫ሺ፪፻፲፯ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፭ ህዳር ፲፭ ፲፱የኝ፱ ፫ . " የኢንፎርሜሽን ሥርዓት " ማለት ኢንፎርሜሽን ለመሰብሰብ ፣ ለመተንተን ፣ ለመጠበቅና ለተጠቃ ሚዎች ለማስተላለፍ የሚያስችል ሥርዓት ነው ፤ ፬ ' የኢንፎርሜሽን ሥርዓት ደህንነት " የኢንፎሜሽን ሥርዓትን ሆን ተብሎ ከታቀደ በስህተት ከሚፈጠር ያልተፈቀደ አጠቃቀም በተከማቸበት ፣ በሚተነተንበት ወይም በሚተላለፍበት ወቅት ከሚከሰት መረጃውን ከሚቀይር እንዲሁም የተፈቀደለት ተጠቃሚ አገልግሎት እንዳያገኝ ከሚያግድ ያልተፈቀደለት አገልግሎት እንዲያገኝ ከሚያደርግ መከላከል ድርጊቱን ለመከታተል ፣ ለመመዝገብና ለመውሰድ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ይጨምራል ፤ ፭ " ኢንፎርሜሽን ሽበራ " ማለት የኢንፎርሜሽን መረብን በመጠቀም ሽብርና አመጽን የመቀስቀስ ተግባር ነው ፤ ፮ . የኢንፎርሜሽን ጦርነት " ማለት ኢንፎሜሽንን ፣ ኢንፎርሜሽንን መሠረት ያደረገ የውሳኔ አሰጣጥ ሃደትን ፣ የኢንፎርሜሽን ሥርዓትና ኮምፒውተር ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገን መረብ ሆን ተብሎ ከሚታቀድ ጥቃት የመከላከልና ኣፀፋዊ ምላሽ የመስጠት ተግባር ነው ፤ ፯ . ' የኢንፎርሜሽን መረብ " ማለት በኢንተርኔት ወይም ኮምፒውተሮችን በማስተሳሰር ኢንፎር የማጓጓዝ የማከማቸትና የማሰራጨት ሥርዓት ነው ፤ “ የኢንፎርሜሽን ደህንነት መንግሥታዊም መንግሥታዊ አካላት የኢንፎርሜሽን መረብ አማካይነት ሊደርስ የሚችል አደጋን የማስወገድ ወይም የመቀነስ ተግባር ነው ፤ ፱ " ኤሌክትሮ ማግኔቲክ ኢነርጂ " ማለት ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ከሆኑ አካላት የሚመነጭ የኒውክሌር ሳይጨምር ለግንኙነት ፣ አሰባሰብና ለኢንፎርሜሽን ውጊያ ጥቅም ላይ የሚውል የጨረር ኃይል ነው ፤ ፲ " ሪሞት ሴንሲንግ " ማለት በሳተላይት ወይም በሌሎች በራሪዎች ላይ በሚገጠም የመረጃ ማሰባሰቢያ አነፍናፊ መሣሪያዎች በመጠቀም የሚካሄድ የኢንፎርሜሽን ኣሰባሰብ ዘዴ ነው ፤ ፲፩ . " ኦፕትሮኒክስ " ማለት የተወሰነ የኤሌክትሮ ማግኔቲክ ኢነርጂ ክልልን በመጠቀም በካሜራ አማካይነት መረጃ የመሰብሰብ ዘዴ ነው ፤ ፲፪ . " ክሪፕቶሎጂ " ማለት የኢንፎርሜሽን ደህንነትና እርግጠኝነትን ለማረጋገጥ ሲባል የሚከናወን የሶፍትዌርና ሀርድዌር ዲዛይንና የኮምፒውተር ቋንቋን የሚመለከት ሃሳባዊ ቀመር ነው ፡፡ ፫ መቋቋም ፩ . የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ( ከዚህ በኋላ " ኤጀንሲ " እየተባለ የሚጠራ ) የህግ ሰውነት ያለው ራሱን የቻለ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሆኖ በዚህ ደንብ ተቋቁሟል ፡፡ ፪ . ኤጀንሲው ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሆናል ፡፡ ገጽ ፫ሺ፬፻፵፰ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፩ ህዳር ፲፭ ፲፱፻፱ ፬ . ዋና መሥሪያ ቤት የኤጀንሲው ዋና መሥሪያ ቤት በአዲስ አበባ ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በማናቸውም ሥፍራ ቅርንጫፍ ሊኖረው ይችላል ። ፭ ዓላማ የኤጀንሲው ዓላማ ሀገሪቱ የኢንፎርሜሽንና የኢንፎርሜሽን መረብ ቴክኖሎጂንና ቴሌኮሙኒኬሽንን ለብሄራዊ ደህንነቷ ስጋት ሳያስከትል የሰላም ፣ የዲሞክራሲና የልማት መርሃ ግብሮቿን ተግባራዊ ለማድረግ እንድትጠቀምበት ማስቻል ይሆናል ፡፡ ፮ . ሥልጣንና ተግባር ኤጀንሲው የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል ፤ ፩ . የኢንፎርሜሽንና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት በሚመለከት መንግሥትን ማማከርና ፖሊሲዎችና ህጎችን አፈጻጸም መከታተል ፤ ፪ . በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነትና የኢንፎርሜሽን ጦርነት ቴክኖሎጂዎች መስክ በጥናትና ምርምር ላይ የተመሠረተ ሀገራዊ አቅም መፍጠርና በዘርፉም የጥናት ፣ የዲቨሎፕመንት ፣ የዲዛይን ፣ የሙከራና ሥራዎችን መንግሥታዊ መሰል ተቋማት ጋር አቀናጅቶ መፈጸም ፤ የኮምፒውተር መረብ ፣ የኢንፎርሜሽን ስርዓትና የኤሌክትሮ ማግኔቲክ አጠቃቀምንና የኢንፎርሜሽን ጦርነትን በሚመለከት የፖሊሲ ፣ የህግ ፣ የዕውቀትና የሌሎች ጉዳዮች ብሔራዊ ቅንጅት የሚፈጠርበትን ሁኔታ ማመቻቸት ፤ ፬ በሲግናልና ቴክኒካል ኢንፎርሜሽን እንዲሁም በክሪፕቶሎጂ በጥናትና ምርምር ላይ የተመ ለተለያዩ መንግሥታዊ የጸጥታ ተቋማት መስጠት ፤ ኙ የሪሞት ሴንሲንግ ካሜራዎችንና የተለያዩ ማግ ግራቪቲና የኤሌክትሮ ኦፕቲካል አነፍናፊዎችን በመጠቀም የሚደረግ ማንኛውም የዳታ አሰባሰብ ፣ ትንተና ፣ ሥርጭትና ዳታ ባንክ የመገንባት ተግባር ብሔራዊ የመረጃ ደህንነት ደረጃዎችን ጠብቆ መከናወኑን መከታተል ፤ ፮ . በብሔራዊ ደረጃ የክሪፕቶሎጂ ጥናት ፣ ዲዛይንና ዲቨሎፕመንት ሥራዎች በማከናወንና በቴክኖ ሉጂ ሽግግር አማካይነት ብሔራዊ የመረጃ ደህንነት ደረጃዎች መጠበቃቸውን ማረጋገጥ ፤ ፯ . አለም አቀፋዊም ሆነ ሀገራዊ የኢንፎርሜሽን ሥርዓትን በመጠቀም በሀገሪቱ መንግሥታዊ ሥርዓትና ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ የወንጀልና ተግባሮችን መከታተልና በአጥፊዎቹ ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መተባበር ፤ ፰ . በኦፕቶሮኒክስ ፣ በሪሞት ሴንሲንግ ቴክኖሎጂዎችና የአየርና የየብስ ቅኝት ሥርዓቶች ኣማካይነት ከመሬት በላይና በታች አመልካች ዳታዎች ለመሰብሰብ ፣ ለመተንተን ፣ ለማከማ ለማሠራጨት የሚያስችል በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስርዓት እንዲኖር ማድረግ ፤ ተቋማትን ኔትወርክ ፣ ሶፍትዌርና ሃርድዌር ቴክኖሎጂ አመራረጥ ፣ የክሪፕቶሎጂ አልጎሪዝም ስታንዳርድ ፣ ኮንፍግሬሽን ፣ አጠቃ ቀምና ደህንነት በሚመለከት በምርምር የታገዘ ገጽ ፫ሺ፪፻፩ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፭ ህዳር ፲፭ ፲፱፻፱ የቁልፍ ተቋማትን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህን ነት አጠባበቅ ጥንካሬና ተጋላጭነትን ለመለካት የሚያስችል የሪስክ አሰስመንት ጥናትና የሙከራ መሥራትና የእርምት እርምጃዎች እንዲወስዱ ማገዝ ፤ ፲፩ . በመንግሥታዊም ሆነ በግል ተቋማት ሀገራዊ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል ተጋላጭ ጎኖችን ለመከላከል የሚረዳ ከፌደራል የኢንፎርሜሽን ደህንነት ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ የኢንፎርሜሽን ስታንዳርድና ፕሮሲጀር እንዲዘጋጁና እንዲተገበሩ መደገፍ ፤ ፲፪ . የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አጠባበቅ ንቃተ የሚያሳድጉ የትምህርትና ፕሮግራሞች መቅረጽና መስጠት ፤ ፲፫ ወደ ሀገር የሚገቡና ከሀገር የሚወጡ የኢንፎር ኮሙኒኬሽን ፣ ሴንሰሮች ፣ የኢንፎርሜሽን ጦርነትና የክሪፕቶሎጂ ቴክኖሎ ጂዎች ከብሔራዊ ደህንነት አንጻር ሊያስከትሉ የሚችሉትን የመንግሥታዊ የፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መከታተል ፤ ፲፬ ብሔራዊ የኢንፎርሜሽን ደህንነትን በተሟላ መልኩ ለመጠበቅ የሚችል የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ፤ ፲፭ . ለሚሰጠው ኣገልግሎት ተመጣጣኝ ማስከፈል ፧ ፲፮ የንብረት መዋዋል ፣ በስሙ መከሰስና መክሰስ ፤ ፲፯ . ዓላማውን . ለማስፈፀም የሚያስፈልጉ ሌሎች ተግባሮችን ማከናወን ፡፡ ፯ . የኤጀንሲው አቋም ኤጀንሲው ፣ ፩ . እንዳስፈላጊነቱ በመንግሥት የሚሰየም አማካሪ ፪ . በመንግሥት የሚሾሙ አንድ ዋና ዳይሬክተርና ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ፣ እና ፫ አስፈላጊው ሠራተኞች ፣ ይኖሩታል ፡፡ ፰ . የዋናው ዳይሬክተር ሥልጣንና ተግባር ፩ . ዋናው ዳይሬክተር የኤጀንሲው አስፈጻሚ የኤጀንሲውን ይመራል ፣ ያስተዳድራል ፡፡ ፪ . በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) የተመለከተው አጠቃላይ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ ፣ ዳይሬክተር ፧ ሀ ) በዚህ ፮ የተመለከቱትን የኤጀንሲውን ሥልጣንና ተግባራት በሥራ ላይ ያውላል ፤ ለ ) የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ህጎችን መሠረታዊ ዓላማዎች ተከትሎ በመንግሥት በሚፀድቅ መመሪያ መሠረት የኤጀንሲውን ሠራተኞች ይቀጥራል ፣ ያስተዳድራል ፤ ሐ ) የኤጀንሲውን ፕሮግራምና በጀት ያዘጋጃል ፣ ሲፈቀድም በሥራ ላይ ያውላል ፤ መ ) ለኤጀንሲው በተሪ ገንዘብ ወጭ ያደርጋል ፤ ሠ ) ከሦስተኛ ወገኖች ጋር በሚደረጉ ግንኙነቶች ሁሉ ኤጀንሲውን ይወክላል ፤ ረ ) የኤጀንሲውን አፈጻጸምና አዲስ ኣበባ ታህናዊ ገጽ ፭ሺ፭፻ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፭ ህዳር ፲፭ ፲፱፻ህ ዋናው ዳይሬክተር ለኤጀንሲው የሥራ ቅልጥፍና ባስፈለገ ሥልጣንና ተግባሩን ለኤጀንሲው ኃላፊዎችና ሠራተኞች በውክልና ሊያስተላልፍ ይችላል ፡፡ ፬ . በጀት የኤጀንሲው በጀት በመንግሥት ከሚመደብ ገንዘብና በዚህ ደንብ አንቀጽ ፮ ( ፲፭ ) መሠረት ከሚሰበሰብ የአገልግሎት ክፍያ የሚውጣጣ ይሆናል ፡፡ ፲ የሂሣብ መዛግብት ኤጀንሲው የተሟሉና ትክክለኛ የሆኑ የሂሣብ መዛግብት ይይዛል ፡፡ የኤጀንሲው የሃሳብ መዛግብትና ገንዘብ ነክ ሰነዶች በየዓመቱ በዋናው ኦዲተር ወይም እርሱ በሚሰይመው ኦዲተር ይመረመራሉ ፡፡ ፲፩ . ደንቡ የሚፀናበት ጊዜ በፌዴራል ከወጣበት ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል ፡፡ • ፮ ቀን ፲፱፻፱ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?