×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
አዋጅ ቁጥር ፫፻፮/፲፱፻፶፮ ዓም የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ 3 ነጥብሊክ ሕገ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አሥረኛ ዓመት ቁጥር አዲስ አበባህዳር ፫ ቀን ፲፱፻፲፮ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፫፻፳፮ / ፲፱፻፲፮ ዓም የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ .. ገጽ ፪ሺ፬፻፴፱ አዋጅ ቁጥር ፫፻፳፮ / ፲፱፻፲፮ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር ፳፯ ፲፱፻ጽ፱ አንዳንድ | WHEREAS , it has been necessary to amend some provisions ድንጋጌዎችን ማሻሻል ፣ እና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት | of the commercial Registration and Business licensing አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች ተጨማሪ ድንጋጌዎችን ማካተት በማስ | Proclamation No. 67/1997 and to include some additional በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ መንግሥት አንቀጽ ፶፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ፩ አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቁጥር ፫፻፸፮ ፲፱፻፲፮ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ . ማሻሻያ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር ፳፯ ፲፱፻፵፬ / እንደተሻሻለ ከዚህ እንደሚከተለው ተሻሽሏል ። ፩ በአዋጁ አንቀጽ ፭ ላይ የሚከተሉት ንዑስ አንቀጽ ( ፰ ) ፣ ( ፱ ) ፣ ( ፲ ) እና ) ፲፩ ) ተጨምረዋል ። ፰ ) የንግድ ማህበራት መስራቾች ወይም አባላት በተፈ ረሙና በንግድ መዝገብ በገቡ መመስረቻ ጽሑፎቻ ቸውና መተዳደሪያደንቦቻቸውላይ ከሚያደርጓቸው ማናቸውም ማሻሻያዎቻቸው በስተቀር ለንግድ ምዝገባ ከመቅረባቸው በፊት የመመስረቻ ጽሑፎቻ F ውናና የመተዳደሪያ ደንቦቻቸውን አግባብ ያለው ባለሥልጣን ለውልና የሰነዶች ምዝገባ ጽ / ቤት በሚልካቸው ደረጃቸውን የጠበቁ የመመስረቻ ጽሑፍና የመተዳደሪያ ደንብ ናሙናዎች መሠረት መፈራረም አለባቸው ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ ፰ሺ፩ ገጽ ፪ሺ o የሣ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፱ ኅዳር ፫ ቀን ፲፱፻፲፮ ዓ.ም። የንግድ ማህበር መስራቾች ወይም አባላት የመመስረቻ | 9 ) Before signing their memorandum and Articles of ጽሑፎቻቸውን ወይም መተዳደሪያ ደንቦቻቸውን ከመፈራረ ማቸው በፊት የንግድ ማህበሩን ስም በተመለከተ በቅድሚያ ኣግባብ ያለው ባለሥልጣን ስሙ በሌላ ነጋዴ ያልተያዘ መሆኑን ሊያረጋግጥላቸው ይገባል ። 1. በትራንስፖርት ንግድ ሥራ ተሰማርቶ የነበረ ግለሰብ ነጋዴ ወራሾች በንግድ ስራው ለመቀጠል የንግድ ማህበር ለማቋቋም ያልፈለጉ ከሆነ ካወራሾቹ አንዱ በሌሎቹ በሚሰጠው ውክልና መሠረት በንግድ መዝገብ መመዝገብ ይችላል ። ፲፩ . በንግድ ማህበር ውስጥ በዓይነት የሚደረግ መዋጮን ግምት የንግድማህበሩ መስራቾች ወይም አባላት ባደረጉት ስምምነት የተወሰነ መሆኑ በመመስረቻ ጽሑፉውስጥ መጠቀስ አለበት ። ፪ ) የአዋጁ አንቀጽ ፰ ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀጽ ፰ ተተክቷል ። የንግድ ማህበራት የሕግ ሰውነት የንግድ ማህበራት በንግድ ሕግ ቁጥር ፳፯ ፡ ፪፻፲፱ ፣ ፪፻፳ ፣ ፪፻፳፫ እና ፪፻፳፬ እንደተደነገገው ስለ መመስረታቸው ወይም በመመስረቻ ጽሑፎቻቸው ላይ ስለሚደረጉ ማሻሻያዎች የጋዜጣ ማስታወቂያ ሳያስፈልጋቸው በንግድ መዝገብ በመመዝገብ የሕግ ሰውነት ያገኛሉ ። ፪ ) የንግድ ማህበራትን የንግድ ምዝገባ ሦስተኛ ወገኖች እንዲያውቁት መዝገቡ ክፍት ይደረጋል ። የአዋጁ አንቀጽ ፬ ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀጽ ፬ ተተክቷል ። ፱ ) ምዝገባው ስለሚፀናበት ጊዜ ማንኛውም የንግድ ምዝገባ የሚፀናው አመልካቹ በንግድ መዝገብ ከተመዘገበበት ዕለት ጀምሮ ነው ። የአዋጁ አንቀጽ ፰ ንዑስ አንቀጽ ( ፭ ) ተሰርዟል ። የአዋጁ አንቀጽ ፳፪ ፣ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) እና ( ፫ ) ተሰርዘው በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) እና ( ፫ ) ተተክ ተዋል ። ፪ ) ፈቃድ ለተጠየቀበት የንግድ ሥራ አግባብ ያለው የመንግሥት መሥሪያ ቤት በመመሪያ የሚወሰነውን መስፈርት ስለማሟላቱ በአመልካቹ የተፈረመ ማረጋገጫ መቅረብ አለበት ። አግባብ ያለው ባለሥል ጣንም ስለመመሪያው አፈፃፀም ለሚመለከተው መሥሪያ ቤት ያሳውቃል ። ፫ ) ከላይ በንዑስ ቁጥር ( ፪ ) የተጠቀሰው ቢኖርም የሙያ ብቃት ወይም የባለቤትነት ማረጋገጫ ሊቀርብ ባቸው የሚገቡ የንግድ ሥራዎችንና ይህንኑ ማረጋገጫ የሚሰጡ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን የሚኒስትሮች ምክር ቤት በደንብ ይወስናል ። 6 ) የአዋጁ አንቀጽ ፳፫ላይ የሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) ተጨምሯል ። ፫ ) በትራንስፖርት ንግድ ሥራ ተሰማርቶ የነበረ ግለሰብ ነጋዴ ወራሾች በንግድ ስራው ለመቀጠል የንግድ ማህበር ለማቋቋም ያልፈለጉ ከሆነ ከወራሾቹ አንዱ በሌሎቹ ወራሾች በሚሰጠው ውክልና መሠረት በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) መሠረት በንግድ መዝገብ ከተመዘገበ በኋላ በወኪሉ ስም የንግድ ፈቃዱ ይሰጣል ። ፯ ) የአዋጁ አንቀጽ ፳፭ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) ተሰርዞ በሚከ ተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) ተተክቷል ። ገጸ ፪ሺ፱የ፩ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፱ ኅዳር ፫ ቀን ፲፱፻፲፮ ዓ.ም ፫ ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) በተመለከተው ጊዜ ውስጥ የንግድ ሥራ ፈቃዱን ሳያሳድስ የቀረ ሳለፈቃድ በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ውስጥ ማለትም ከጥር ፩ ቀን እስከ ሰኔ ፴ ቀን ከፈቃድ ማሳደሻው በተጨማሪ ለዘገየበት ለጥር ወር ብር 2,500.00 ( ሁለት ሺህ አምስት መቶ ) እና ለሚቀ ጥለው እያንዳንዱ ወር ብር 1,500.00 ( አንድ ሺህ አምስት መቶ ) ቅጣት በመክፈል የንግድ ፈቃዱን ያሳድሳል ። ፰ ) የአዋጁ ኣንቀጽ ፳፰ ንዑስ አንቀጽ ( ፬ ) እና ( ፮ ) ተሰርዘው በሚከተሉት አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እና ( ፮ ) ተተክ ተዋል ። ፬ ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ( ሠ ) ምክንያት ካልሆነ በስተቀር በሌሎች ማናቸውም ምክንያቶች የንግድ ሥራ ፈቃድ የተሰረዘባቸው ነጋዴዎች ያንኑ የንግድ ሥራ ፈቃድ እንደ አዲስ ለማውጣት የሚችሉት ከአንድ ዓመት በኋላ ነው ። ፮ ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፭ ) መሠረት አግባብ ላለው ባለሥልጣን የንግድ ፈቃዱን ተመላሽ የሚያ ደርግ ነጋዴ ወይም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) መሠረት የተሰረዘበትን ያንኑ የንግድ ሥራ ፈቃድ እንደ አዲስ ለማውጣት ሲመጣ ወይም በዚህ አዋጅ ኣንቀጽ ፳፬ መሠረት ምትክ የንግድ ሥራ ፈቃድ እንዲሰጠው የሚጠይቅ ነጋዴ ተመላሽ በተደረገው ወይም በተሰረዘው ወይም በሚተካው የንግድ ሥራ ፈቃድ ለተጠቀመበት ጊዜ የግብር ክሊራንስ ማቅረብ አለበት ። ፬ ) የአዋጁ አንቀጽ ፳፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) ተተክቷል ። ፫ ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) መሠረት ጥያቄው የቀረበለት አግባብ ያለው ባለሥልጣን ኣመልካቹን ለጠፋው የንግድ ፈቃድ የኃላፊነት ግዴታ በማስፈ ረምና በደንቡ የተመለከተውን ክፍያ በማስከፈል ምትክ የንግድ ሥራ ፈቃድ ይሰጠዋል ። ፲ የአዋጁ አንቀጽ ፴፭ ላይ የሚከተለው አዲስ ንዑስ ኣንቀጽ ( ፫ ) ተጨምሯል ። ፫ ) የሚመለከተው የሴክተር መሥሪያ ቤት ነጋዴው ፈቃድ ከተሰጠበት መስፈርት ውጭ ሲሰራ ሲገኝ ወይም ጥፋት ሲፈጽም መወሰድ ስለሚገባው እርምጃ አግባብ ላለው ባለሥልጣን ማሳወቅ አለበት ። ፫ ኣዋጁ የሚፀናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከህዳር ፫ ቀን ፲፱፻፲፮ ዓም ጀምሮ የፀና ይሆናል ። አዲስ አበባ ኅዳር ፫ ቀን ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. ግርማ ወልደጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?