×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
የሰንደቅ ዓላማና ዓርማ አዋጅ ቁጥር ፲፮/፲፱፻፹፰

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ሁለተኛ ዓመት ቁጥር ፪ አዲስ አበባ ጥር ፳፰ ቀን ፲፱፻፰፰ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፲፮ / ፲፱፻፳፰ ዓም የሰንደቅ ዓላማና አርማ አዋጅ . ገጽ ፲፬ አዋጅቁጥር ፲፮ / ፲፱፻፰ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሰንደቅ ዓላማና ዓርማ አዋጅ ስለ ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማና ዓርማ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፪ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እና ( ፪ ) የተደነገገ በመሆኑ ፤ ለሕገ መንግሥቱ ድንጋጌ አፈጻጸም ሰንደቅ ዓላማንና ዓርማን የሚመለከቱ ዝርዝር ጉዳዮችን የሚወስን ሕግ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፤ | በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ | መንግሥት አንቀጽ ፵፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ክፍል አንድ ፩ . አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የሰንደቅ ዓላማና ዓርማ አዋጅ ቁጥር ፲፮ | ፲፱፻ጅቷ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ክፍል ሁለት ስለ ሰንደቅ ዓላማና ብሔራዊ ዓርማ ፪ : የሰንደቅ ዓላማ ምንነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሰንደቅ ዓላማ ( ከዚህ በኋላ “ ሰንደቅ ዓላማው ” እየተባለ የሚጠራ ) የሪፐ ብሊኩ ሉዓላዊነትና የሕዝቦች በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አንድነት መግለጫ ነው ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ• ቸሺ፩ ገጽ ፲፭ ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፬ ጥር ፳፰ ቀን ፲፱፻ዥ፰ ዓ•ም• _ Negarit Gazeta - No . 4 6 February 1996 Page 95 ፫ የሰንደቅ ዓላማው ቀለማትና ቅርጽ ፩ ሰንደቅ ዓላማው ከላይ አረንጓዴ ፡ ከመሃል ቢጫ ፡ ከታች ቀይ ሆኖ በመሃሉ ክብ በሆነ ሰማያዊ መደብ ላይ የተቀረጸ ብሔራዊ አርማ ይኖረዋል ። ፪ ቀለማቱ ብሩህና መሠረታዊ ይሆናሉ ። ፫ ቀለማቱ ኣግድም የተዋቀሩና እኩል ስፋት የሚኖራቸው ይሆናሉ ፤ የሰንደቅ ዓላማው ወርድ የቁመቱ እጥፍ ይሆናል ። ፬ . የዓርማው ቅርጽ ክብ በሆነ ሰማያዊ መደብ ላይ ፦ ሀ ) ከየአቅጣጫው መጥተው የሚገናኙ ቀጥታና እኩል የሆኑ ቢጫ መስመሮች ይኖረዋል ። ለ ) ቀጥታና እኩል ከሆኑት መስመሮች የተዋቀረ ኮከብ ይኖረዋል ። ሐ ) ቀጥታና እኩል በሆኑት መስመሮች መጋጠሚያ ላይ የሚፈነጠቅ ቢጫ ጨረር ይኖረዋል ። ፩ የሰንደቅ ዓላማው ቀለማት ትርጉም የሰንደቅ ዓላማው ቀለማት የሚከተለው ትርጉም ይኖራቸዋል ፤ | ፩ አረንጓዴው የሥራ ፡ የልምላሜና የዕድገት ምልክት ነው ፤ | 2 ) the yellow for hope , justice and equality , and . ፪• ቢጫው የተስፋ ፡ የፍትሕና የእኩልነት ምልክት ነው ፤ ፫ ቀዩ ለነጻነትና ለእኩልነት መስፈን የሚደረግ የመስዋዕት ነትና የጀግንነት ምልክት ነው ። ፬ ፡ የዓርማው ትርጉም : ክብ ሰማያዊ መደብ ፡ ሰላምን ያመለክታል ። ፭ የዓርማው ትርጉም ፩ : ቀጥታና እኩል የሆኑት መስመሮች ፤ . የብሔሮች ፡ የብሔረሰቦችና የሕዝቦች እንዲሁም የሃይማ ንፍ ኖቶችን እኩልነት ያመለክታሉ ። ። ፪ ቀጥታና እኩል ከሆኑት መስመሮች የተዋቀረው ኮከብ ፣ የኢትዮጵያ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በመፈ ቃቀድ የመሰረቱትን አንድነት ያመለክታል ። ። ፫ ቢጫ ጨረር ፤ በመፈቃቀድ አንድነት ለመሠረቱት ብሔር ፣ ብሔረሰቦች | የፈነጠቀውን ብሩህ ተስፋ ይጠቁማል ። ማን ፮ ፡ የሰንደቅ ዓላማው ስዕላዊ መልክ የሰንደቅ ዓላማው ስዕላዊ መልክ እንደሚከተለው ነው ፡ ገጽ ፲፮ ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፬ ጥር ፳፰ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ . ም . Negarit Gazeta - No . 4 6 February 1996 – Page 96 ፯ የሰንደቅ ዓላማ አወጣጥ የሰንደቅ ዓላማውን መውለብለብ የሚያግድ ከአቅም በላይ | . የሆነ ምክንያት ካላጋጠመ በስተቀር ፤ ፩ . በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚኒስትሮችምክር ቤት ከላይ እስከ ታች ባሉ የክልል የሥልጣን ኣካላት ጽሕፈት ቤቶች ' በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ፡ በሌሎች ኣስፈጻሚ አካላት ጽ / ቤቶች ፡ በፍርድ ቤቶች ፡ በትምህርት ቤቶች ፡ በመከላከያ ድርጅቶች ፡ በፖሊስና ፡ በጠረፍ ጥበቃ ተቋሞች በሪፐብሊኩ ኤምባሲዎችና በአምባሳደሮች መኖሪያ ቤት ሕንጻዎች ሰንደቅ ዓላማ በየቀኑ ይወጣል ፤ ጀ የሪፐብሊኩ የንግድ መርከቦች እና ጀልባዎች በየቀኑ ሰንደቅ ዓላማ ያወጣሉ ፤ ፫ . በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ያልተመለከቱ የመን ግሥት መሥሪያ ቤቶች በብሔራዊ በዓል ቀን ሰንደቅ ዓላማ ያወጣሉ ፤ ሰንደቅ ዓላማ የሚወጣው በሚከተሉት ሥፍራዎች ይሆናል ፤ . ሀ ) በፌዴሬሽን ምክር ቤት በቅጥር ግቢው ኣደባባይ ለ የሪፐብሊኩ ርዕሰ ብሔርና ርዕሰ መስተዳድር በጽሕ ፈት ቤቱና በመኖሪያ ቤቱ ሕንጻዎች ላይ ፤ ሐ የሪፐብሊኩ ርዕሰ ብሔርና ርዕሰ መስተዳድርና አም ባሳደሩ የሚጓዝበት ተሽከርካሪ ፡ አውሮፕላንና 8 . Size of the Flag ተንሳፋፊ ላይ ፧ ፰ የሰንደቅ ዓላማው መጠን በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፫ ( ፫ ) የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ፡ ሰንደቅ ዓላማው የሚከተለው መጠን ይኖረዋል ፤ ፩ በከፍተኛ አደባባይ የሰንደቅ ዓላማው መጠን ፪፻፲ በ፬፻፳ ሴሜ ፡ የሰንደቁ ቁመት ከ፲፭ እስከ ፲፰ ሜትር ፡ ፪ በመካከለኛ አደባባይ የሰንደቅ ዓላማው መጠን የፃ በ፫፻ ሴሜ ፡ የሰንደቁ ቁመት ከ፬ እስከ ፲፭ ሜትር ፤ ፫ በመሥሪያ ቤቶች በከፍተኛ የትምህርት ተቋሞችና ድርጅቶች አደባባይ የሠንደቅ ዓላማው መጠን ፳፻፴፭ በ፪፻ኛ ሴሜ • የሰንደቁ ቁመት ከ፫ እስከ ፲፪ሜትር ፤ ፩ በትልልቅ የመንግሥት ህንጻዎች ላይ የሰንደቅ ዓላማው መጠን ፩፻፴፭ በ፪፻ኛ ሴሜ• የሰንደቁ ቁመት ፭ ማትር ! ኛ በትልልቅ ሕንጻዎች ምድር ቤት ውስጥ የሚገኙ ድርጅ ቶችና የንግድ ቤቶች የሠንደቅ ዓላማው መጠን ፳፻፭ በ፪፻፲ ሴሜ ፡ የሰንደቁ ቁመት ማትር ! ፮ በከፍተኛ መርከቦች ላይና በሰልፍ ጊዜ በክብር ዘብ የሚያዘው የሠንደቅ ዓላማው መጠን ፳፭ ባ፪፻፲ ሌማ የሠንደቁ ቁመት ፪፻፴ ሴማ ፤ ፯ ለውጭ ሀገር እንግዳ አቀባበልና ለበዓላት በየመንገዱ ለሚውለበለብ የሠንደቅ ዓላማው መጠን ¶ ሰ፳፻፰ ሴሜ ፡ የሰንደቁ ቁመት ፪ ሜትር ፤ ፰ በመካከለኛ መርከቦች ላይ የሠንደቅ ዓላማው መጠን በ፩፻ዊ ሴሜ ፡ የሰንደቁ ቁመት ፪ ሜትር ፤ ፱ በርእሰ ብሔር በርእሰ መስተዳድሩና በአምባሳደሮች ጽሕፈት ቤት ጠረጴዛ ላይ የሰንደቅ ዓላማው መጠን ፳፩ በ፵፪ ሲሜ ፡ የሰንደቁ ቁመት ፵ ሌማ ! ፲ . ርእሰ ብሔር ' ርእሰ መስተዳድሩና አምባሳደሮች በሚጓ | ዙበት መኪና ላይ የሚውለበለበው ሰንደቅ ዓላማ ! የቁመቱና የወርዱቅንብርሴሾ ) ፫ላ፬ሆኖብ በኋላ ና | . ገጽ ፲፯ ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፩ ጥር ፳፰ ቀን ፲፱፻ዥ፰ ዓም• _ Negarit Gazeta - No . 6February 1996 Page 97 ፱• የሰንደቅ መትከያ ሥፍራ በአደባባይ የሚውለበለብ ሰንደቅ ዓላማ የሚተከለው በተቻለ መጠን ከመሥሪያ ቤቱ ህንጻ ፊት ለፊትና መሃል ለመሃል ይሆናል ። ፲ . የሰንደቅ ልሣን የማናቸውም ሰንደቅልሣን ( ጫፍ ) የጦርአምሳልይኖረዋል ። ፲፩ : ሰንደቅ ዓላማው የሚወጣበትና የሚወርድበት ጊዜ ፩ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) እና የተመለከቱት እንደተጠበቁ ሆነው በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፯ ( ፩ ) በተጠ ቀሱት መሥሪያ ቤቶች እንዲሁም በመርከቦችና ጀልባዎች ላይ ሰንደቅ ዓላማው ከጠዋቱ በ፲፪ ሰዓት ወጥቶ ከምሽቱ ፲፪ ሰዓት ይወርዳል ። ሆኖም የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ በታወጀባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የመከ ላከያ ሠራዊት አሀዶች ሁኔታው እስካልተለወጠ ድረስ መደበኛውን ሰዓት ጠብቅው ሰንደቅ ዓላማውን ማውጣትና ማውረድ አይገደዱም ። . ፪ በትምህርት ቤቶች ሰንደቅ ዓላማው የሚወጣው ጠዋት ተማሪዎች ተሰልፈው ትምህርት ከመጀመሩ በፊት ይሆናል ፤ የሚወርደውም የቀኑ ትምህርት ሲያበቃ ይሆናል ። ፫ በበዓላት ወቅት ሰንደቅ ዓላማው በዋዜማው ወጥቶ በበዓሉማግስት ይወርዳል ። ፲፪ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሰንደቅ ዓላማ | ከዚህ በላይ በተደነገጉት አንቀጾች መሠረት አረንጓዴ ቢጫ ቀይና ክብ ሰማያዊ ቀለማት ኖሮት በመሀከሉ በዚህ አዋጅ የተዘረዘረው ዓርማ ያለው ብቻ ነው ። ፲፫ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ይህንን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሰንደቅ ዓላማ የሚገባውን ክብር | የመስጠትና የማክበር ኃላፊነትና ግዴታ አለበት ። ክፍል ሦስት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ፲፬ ደንብ የማውጣት ሥልጣን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህን አዋጅ ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊ የሆነ ደንብ ለማውጣት ይችላል ። ፲፭ መመሪያ ስለማውጣት በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፬ መሠረት የሚወጣውን ደንብ ተከትለው የሚከተሉት መሥሪያ ቤቶች የአፈጻጸም መመሪ ያዎች ለማውጣት ይችላሉ ፤ ፩ . የመከላከያ ሠራዊት አሀዶችን በሚመለከት የሀገር | መከላከያ ሚኒስቴር ፡ ፪ የንግድ መርከቦችንና ጀልባዎችን በሚመለከት የትራንስ ፖርትና መገናኛሚኒስቴር ፫ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ ዎችንና ቆንስላዎችን በሚመለከት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ። ገጽ ፲፮ ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፬ ጥር ፳፰ ቀን ፲፱፻፰፰ ዓ - ም ፲፮• የተሻሩ ሕጎች የሚከተሉት ሕጎች በዚህ ኣዋጅ ተሽረዋል ፤ ፩ . የሰንደቅ ዓላማ አዋጅ ቁጥር ፫ ፲፱፻፫ ፣ እና ፪ : የሪፐብሊኩ ዓርማ አዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻ዥ ። ፲፯ አዋጁ የሚጸናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከጥር ፳፰ ቀን ፲፱፻T፰ ዓም ጀምሮ የጸና | ይሆናል ። አዲስ አበባ ፣ ጥር ፳፰ ቀን ፲፱፻ዥ፰ ዓም ዶ / ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?